የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ
 ENG  /     አማ   /    oro  

ኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት ፓርክ

የሚገኙበት ቦታ መረጃ

     በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ልዩ ቦታው ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አጠገብ የሚገኝ ነው፡፡

ለምቶ አገልግሎት የሰጠበት ጊዜ

  ቀደም ሲል ለአብዮቱ እና ለኩባ ሰማዕታት መታሰቢያነት በደርግ ዘመነ መንግስት ትግላችን ሀውልት በሚባል የለማ ሲሆን በ2009 ዓ.ም በቢሮው የማሻሻያ እድሳት ተከናውኖለት ለነዋሪው የመዝናኛ አገልግሎት እየሠጠ ይገኛል፡፡

ልዩ የሚያደርገው

    የኢትዮ-ኩባ የወዳጅነት ፓርክ በውስጡ የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ትግል እና በኢትዮ-ሱማሌ ጦርነት ከኢትዮጵያ ጎን ቆመው የተሰው የኩፓ ወታደሮች ታሪክ የሚዘክሩ ቅርሶች የሚገኙበት ነው፡፡

የልማት ሁኔታው

 

  •  ፓርኩ በማሻሻያ እድሳት ሲለማ ደረጃውን የጠበቀ ዲዛይን የተዘጋለት ሲሆን ልማቱን የሚገልጽ ሳይት ፕላን አለው፡፡
  • ፓርኩ ገጽታውን በማያውክ መልኩ አንደርግራውንድ የመጸዳጃ ቤት የተሰራለት ነው፡፡
  •  ፋውንቴኑ የሚሰራ እና ኤሌክትሮ ሜካኒካ ሲስተሙ የተሟላ ነው፡፡
  •  ለሀይል አቅርቦት አስታማማኝ የሆነ የራሱ ትራንስፎርመር አለው፡፡
  •  ዙሪያ አጥሩ እና የጥበቃ ቤቶቹ የተሟሉ ናቸው፡፡
  • በሀውልቱ ዙሪያ የሚገኘው ፕላዛ ለኢቭንት ማከናወኛ አገልግሎት የሚውል ውብ ስፍራ አለው፡፡
  •  በቂ የሆነ የውሃ አቅርቦት ያለው ነው፡፡
  •  አረንጓዴ ቦታው በእጽዋት የለማ እና ውብ ነው፡፡

 የሚሰጣቸው አገልግሎቶች

  • ለሰርግ፤ለልደት ፣ሌሎች ዝግጅቶችና የመዝናኛ አገልግሎት በደረሰኝን ክፍያ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
  • የበር መግቢያ ትኬት አይቆረጥበትም
  • የፓርኩ አረንጓዴ ቦታ ደረጃውን የጠበቀ ውብ እና ማራኪ ነው፡፡

 


Addis Ababa City Administration Public Recreational Areas Corporation


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን


BULCHIINSA MAGAALAA FINFINNEE Korporeeshinii Bulchiinsa Iddoowwan Bashannanaa ummataa


ስልክ : +251-913558544 / +251-934471822 / +251-934471822
አድራሻ : አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ